Get Mystery Box with random crypto!

አርቲስት መሰረት መብራቴ ለልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል ያሰባሰበችውን 6 ሚሊዮን ብር አስረከ | YeneTube

አርቲስት መሰረት መብራቴ ለልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል ያሰባሰበችውን 6 ሚሊዮን ብር አስረከበች!

አርቲስት መሰረት መብራቴ በአሜሪካን ሀገር በነበራት ቆይታ ያሰባሰበችውን 6 ሚሊዮን ብር ለልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል በዛሬው ዕለት አስረክባለች፡፡

ገንዘቡ የልብ ህመም ላለባቸው 60 ህጻናት ህክምና የሚውል እንደሆነም ተገልጿል።

አርቲስቷ ላለፉት 3 ዓመታት በማዕከሉ በአምባሳደርነት እያገለገለች የምትገኝ ሲሆን ሕክምናን ለማግኘት ወረፋ እየጠበቁ የሚገኙ ህጻናትን ለመታደግ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰብ ስራዎችን እየሰራች ትገኛለች።

በ1981 ዓ.ም የተመሰረተው የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል ላለፉት 32 ዓመታት ከ9 ሺ 500 በላይ ህጻናት ህክምና እንዲያገኙ ማድረጉን መረጃዎች ያሳያሉ።

[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa